• Call Us
  • +251..........

የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው 

ጳጉሜን 3/2017 ዓ.ም

2ኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ጉባዔ በአዲስ አበባ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።

በጉባኤው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅህ ገበየሁ (ዶ/ር) እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት አመራሮች በጉባዔው እየተሳተፉ መሆኑን የኢቢሲ መረጃ ያመለክታል።
 
ጉባዔው “ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት መፍትሄዎችን ማፋጠን፡ የአፍሪካን አረንጓዴ ልማት በፋይናንስ መደገፍ" በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።